1.
የክርስቲያን አርበኞች
ለጦር ስትሄዱ
የየሱስን መስቀል በፊት አስኪዱ
ክርስቶስ ነው መሪያችን
በጦር ሜዳው ላይ
ሂድ ወደ ፊት ለጦርነት
ባንዲራውን እይ
የክርስቲያን አርበኞች
ለጦር ስትሄዱ
የየሱስን መስቀል
በፊት አስኪዱ
2.
እንደ ኃይለኛ ጦር
ናት ቤተክርስቲያን
ጻድቃን በሔዱበት ስንጓዝ ሳለን
አንከፋፈልም አንድም አካል ነን
በተስፋችን በትምህርትም
በችሮታችን
3.
ዘውድ ዙፋን ይጠፋል
መንግሥት ይፈርሳል
ግን ቤተክርስቲያኗ አትናወጥም
በሲኦልም በሮች አትሸነፍም
የክርስቶስ ተስፋ ስላለን
ከቶ አንወድቅም
4.
4.በርቱ እላንት ሰዎች
ባንድ ላይ ስንኖር
አብረን እየዘመርን
የድል መዝሙርን
ክብርና ምስጋና ለንጉሣችን
ለዘልዓለም በደስታ
እንዘምራለን