ታሪኬን ቀይሮ አዲስ ምዕራፍ ጀመርኩኝ
ጌታ ያረገው ሥራ ለእኔስ ገረመኝ
እንደእኔ ማነው ጌታ የደረሰለት ሰው
ይነሳና ያምልከው ማነው ዝም ያሰኘው
1.
የዚች የምድራችን ውበት ሆነ ሀብት
ድሎት ማጣት ሆነ እንዲሁ ማግኘት
አይለየኝም እኔን ከዚህ ከቸር አምላክ
ደስ እያለኝ ሁሌ ጠዋት ማታ ላምልክ
2.
ለጠየቁት ሁሉ ምላሽ ሳያዘገይ
መልስ ይዞ ይቀድመኛል የኔ ጌታ ኤልሻዳይ
ሌላ ማን አለኝ እንዲህ ፈጥኖ ደራሽ
ደስታን አትረፍርፎ እንባዬንም አባሽ
3.
ሁሉን ነገር ተራ በተራ ላውራ ብል
ቃል አጠረብኝ አልበቃ አለኝ
ወደ ፍጥረታቱ ዞር ብዬ ሳያቸው
ሥራው ይገርመኛል አፈጣጠራቸው
4.
ምሥጋናና ክብር ለኢየሱስ ጌታዬ
አቀርባለሁ ዛሬ ይኸው በፊናዬ
በእኔ የጀመረውን ይህን ታምራቱን
መች በዚህ ያበቃል ጌታ እረኝነቱን