1.
የጌታን ታሪክ ንገረኝ
ቃሎቹን በልቤ ጻፍ
የበለጠውን አስታውቀን
ጣፋጭ ቃል ያልተሰማ
መላእክት ሲያመሰግኑህ
በልደት መዝሙራቸው
ከላይ ክብር ሰላም ላምላክ
ለምድርም የምስራች
የጌታን ታሪክ ንገረኝ
ቃሎቹን በልቤ ጻፍ
የበለጠውን አስታውቀን
ጣፋጭ ቃል ያልተሰማ
2.
ብቻውን አርባ ቀን እንዴት
እንደጾመ ንገረኝ
ለኃጢዓታችን ሲፈተን
ድል አደረገ ለኛ
ሥራውን ሁሉ ንገረኝ
ስለ ኃዘኑም ደግሞ
ተጨነቀ ተሰቃየም
ተናቀ ተሳደደም
3.
ስለ መስቀሉ ንገረኝ
በጭንቅ የሞተበትን
ስለ መቃብሩ ንገረኝ
እንደተነሣም ደግሞ
የፍቅሩ ታሪክ ይታያል
ከሌላው ሁሉ ይልቅ
አትራቅ ኃዘን ሲሰማኝ
ፍቅሬ ገዝቶሃል በለኝ