የሚያዋጣኝን አውቄያለሁ
በብርቱ ክንድ ተደግፌያለሁ
የሚያሳፍረኝ የለም አምናለሁ
1.
በአስተማማኝ እጅ ውስጥ አለሁ
ምንጊዜም ቢሆን በማያሰጋው
በእርሱ ታምኜ እኖራለሁ
ለሕይወቴም ዋስትና አለው
2.
ማነው ከእንግዲህ የሚከሠኝ
ብቸኛ ነህ ብሎ የሚኮንነኝ
እኔስ አባት አለኝ የማይለየኝ
3.
ለህዝብና ለእውነት የሚቆም
ክንደ ብርቱ እስከ ዘላለም
መቼም ቢሆን ጥሎኝ የማያውቅ
ጌታ አለልኝ ተግቶ የሚጠብቅ
4.
ከእንግዲህ ለምን እሰጋለሁ
መሠረቴ ምንጊዜም ፅኑ ነው
ለእውነት ብቻ እቆማለሁ
ማዳኑን ለዓለም አወጃለሁ
5.
በምድር በሰማይ የሚያስተማምን
ለሥጋ ለመንፈስ የሚሆን ተገን
ለሁሉ ሚጠቅም የሁሉ ረዳት
ጌታ የሱስ ነው የኔ አባት
6.
በዓለም ዳርቻ ሁሉ እንድንመሰክር
ኃያልነትህን ደግሞ እንድንናገር
እንድንወጣው ታላቁን አደራ
ያ ብዙ አፅናኙ መንፈስ ቅዱስ ይምጣ
7.
አንተ መንፈስ ቅዱስ ሆይ /2X/
ና ጉልበታችንን አፅና /4X/
8.
ተስፋ ለምንቆርጥ በየምክንያቱ
መታመን ያቃተን ሁነናል አቤቱ
በክፉም በደጉም ባንተ እንድንጸና
መንፈስ ቅዱስህን ላክ ይረዳናልና
9.
አንተ መንፈስ ቅዱስ ሆይ /2X/
ና እምነታችንን አፅና/4X/
10.
ሌላውን ለመገሰጽ ራሳች ፈጣን ነን
መንፈሳችንማ ዓይናችን እውር ነው
ራሳችንን ሳናይ ብዙ ተጐድተናል
መንፈስ ቅዱስን ላክ ያስችለናልና
11.
አንተ መንፈስ ቅዱስ ሆይ/2X/
ና ህይወታችንን አፅና/4X/
ና እምነታችንን አፅና/2X/
ና ጉልበታችንን አፅና/4X/