ወደ መነሻ / Back to Home
መዝሙር #126 / Song #126

አንድ ጊዜ ከጌታ አንድ ጊዜ ከአለም

english translation

ምድብ / Category: ምስጋና / Praise
ደራሲ / Author: unknown
ዓመት / Year: 2025
👁️ Views: 1
የክርስቲያን ኑሮ እንደዚህ አይደለም
ይህማ ከሆነ ወንድም ክርስትና
ዋጋ የለሽ ይሆናል አይገኝ ዋስትና
1.
የስም ክርስትና ብይዝ ተሸክሜ
ህይወትን ላያስገኝ ከንቱ ነው ወንድሜ
ያለም ብርሃን ሳልሆን ጨለማ ሆኛለሁ
ዋይ ለእኔ ጌታዬን አሳዝኛለሁ
2.
ስናገር ስዘምር ስሜ ክርስቲያን ነው
ከቤቱ ስወጣ ሥራዬ ሌላ ነው
ዓለም ከዚህ ሌላ ታዲያ ምን ያደርጋል
የእኔስ ክርስትና በምን ይታወቃል
3.
ቢሆን አንድ ባሪያ ለሁለት ጌታ
እንዴትስ ይሆናል ለአንዱ ካልተገዛ
ብርሃን ከጨለማ ምንስ ህብረት አለው
ክርስቲያን በሥራው ጌታን ካልመሰለው
4.
ጌታን እንዳልተወው ህይወትን እሻለሁ
አለምን እንዳለተው ገንዘብን እወዳለሁ
በሰው ዘንድ ሲታይ ትኩስና በራድ
ደቀመዝሙር ነኝ ገንዘብን የምወድ
5.
የአምልኮ መልክ ይዤ ኃይሉን ግን ክጃለሁ
ለተመለከተኝ ክርስቲያን እመስላለሁ
ጌታ የሱስ ልብን የሚመረምረው
የእኔን ክርስትና እርሱ ነው የሚያውቀው
6.
ታላቅ የነገሥታት ንጉስ የሆንከውን ጌታ
ደፋ ቀና ብዬ ዛሬ ልስጥህ ከበሬታ
እንዲሁ ግን በልማድ ስወጣ ስገባ
ድንገት መገለጥ እንዳይሆን አባባ/2X/
ሙላኝ በመንፈስህ ሙላኝ
ንካኝ በመንፈስህ ንካኝ
አንተ ካልነካኸኝ ከንቱ ነው መኖሬ
በደረቀ ህይወት አልደርስም ከሀገሬ
አልገባም ከሀገሬ
7.
ባለብዙ ምህረት ነህ እስካሁን ጠብቀኸኝ
ጀርባህን ሳታዞርብኝ በፍቅር አየኸኝ
ግን አይቀርም አንዴ እኔ ካልተለወጥሁ
ቃልህን ሳላስተውል ወንበር ብቻ ካሞቅሁ/2X/
8.
ቅዱስ መንፈስህን እሻለሁ ደረቅ ህይወት በቃኝ
እስከ ዛሬ ይኸው ስኖር ምንም አልጠቀመኝ
በዘይትህ ሙላኝ እማፀንሃለሁ
የሚያስደስት ፍሬን ያኔ አፈራለሁ--አፈራልሃለሁ
9.
የልቤን መሻቴንና ልመናዬን ሠምተህ
ለውጠኝ እንደምትፈልግ መንፈስህን ሞልተህ
ነቀፋ የሌለኝ ባሪያህ ከሆንኩማ
ቀጥብዬ እገባለሁ ከዚያች ውብ ከተማ/2X/
100%
100%