ወደ መነሻ / Back to Home
መዝሙር #104 / Song #104

ፃዲቁም ይድደቅ እርኩሱም ይርከስ

english translation

ምድብ / Category: ምስጋና / Praise
ደራሲ / Author: unknown
ዓመት / Year: 2025
👁️ Views: 1
የሚባልበት ሰዓቱ ሳይደርስ
ቀን ሳለ ዛሬ በቃሉ እንደግ
በንስሃ ህይወት ወደእርሱ እንለፍ
1.
ሊቀካህናችን ከመቅደስ ሳይወጣ
የምህረት ደጅም ፈጥኖ ሳይዘጋ
ራሳችንን አስጨንቀን በንስሃ እየተዋረድን
ልንጠብቀው ይገባናል
2.
ጌታ ጌታ ሆይ ብቻ እያልን
ፍቃዱን ማድረግ ጭራሽ ተስኖን
በለብታ ህይወት ተዘፍቀን ሳለን
ቀኑ ደርሶብን ጌታ እንዳይተፋን
3.
ቸልተኝነት እኛን አጥፍቶን
ለኃጢኣታችን ንስሃ ረስተን
የጽድቅን ኑሮ ሳንለማመድ
እንደይቋረጥ የእርሱ ማማለድ
4.
እንተራቆትን ዛሬ ተረድተን
አልብሰን ብለን ጌታን ተማጽነን
በጽድቅም መንገድ በእምነት ተጉዘን
ከሚድኑቱ ጐን እንድንገኝ
5.
ኩራዛችንን በዘይት ሞልተን
መብራታችንን ዘውትር አብርተን
ከልባሞቹ ጋር ተደምረን
በሠርጉ እንገኝ ሳይዘጋብን
6.
የአንድ አባት ልጆች ነን 2X
የአንድ ሀገር ዜጐች ነን 2X
በኢየሱስ ፍቅር ተሳስረን
አንድ ሆነናልና ሁላችን
7.
ከእንግዲህ አይሁድ ግሪክ ማለት
የዘር መከፋፈል ልዩነት
ከመካከላችን አስወግደን
እንኑር በአንድ ሀሣብ ተስማምተን
8.
ባካል ብዙ ብልቶች ቢኖሩም
እጅ እግር ዓይን ተብለው ቢጠሩም
ሁሉም በአንድ ላይ ተገጣጥመው
ይሠራሉ ሙሉ አካል ሆነው
9.
እኛ እርስ በርሳችን ተዋደን
የመለየት መንፈስ ተቃውመን
በፍቅር ብንኖር ሁላችን
የእግዛብሔር አምላክ ልጆች ነን
10.
ፍቅር እግዚአብሔር እራሱ ነው
ለምንኖርበትም ብርሃን ነው
ወንድሙን ሚጠላ ነብስ ይገላል
ክብራን ርቆ በጨለማ ይኖራል
100%
100%