ወደ መነሻ / Back to Home
መዝሙር #108 / Song #108

ኮብልላ ነበረች ነፍሴ ከእግዜር መንገድ

english translation

ምድብ / Category: ምስጋና / Praise
ደራሲ / Author: unknown
ዓመት / Year: 2025
👁️ Views: 1
በጣም የበደልኩኝ ኃጢያተኛም ነበርኩ
ግን አዳኜ ከላይ ፍቅር ሠጠኝ ሠላም
ልጁን ለእኔ ልኮ አወጣኝ
1.
ደሙን ለኔ አፍስሶ አዳነኝ/2X/
የማልረባም ብሆን አምላኬን የማላውቅ
ልጁን ለኔ ልኮ አወጣኝ
2.
ተስፋ ቢስ ነበርኩኝ ሊያወጣኝ ሲመጣ
ግን እርሱ ነገረኝ ነፃ እንደምወጣ
ከዚያም አነሳና ክብሩን አቀዳጀኝ
ልጁን ለኔ ልኮ አወጣኝ
3.
ልቤን ደስ ይለዋል ከመረጥኩት ወዲህ
ከማዕበሉ አሁን ወደ እርሱ እጠጋለሁ
ክንዱን ከተደገፍኩ አልፈራም መከራ
ጌታ ለኔ ወርዶ አወጣኝ
4.
ሠማያዊ ደስታ ሠላምን ከሠጠኝ
ጌታ ሆይ ሕይወቴን ለአንተ እሰጣለሁኝ
ከእንግዲህ እጄን ያዝ ከአንተም ጋር አቆመኝ
ልጁን ለኔ ልኮ አወጣኝ
5.
ጉዞ ጀምረናል በመርከቡ የሱስ
ወደ ፅዮን አገር ከእግዚአብሔር ለመድረስ
ብዙ ፌርማታዎች አሉ ከርሱ ሳንደርስ
እልፍ እንቅፋት አለ ከወደቡ እንዳንደርስ
}2xጉዞ 3x ጀምረናል
ከአንተ ጋር ለመኖር ጌታ ሆይ ናፍቀናል
የሱስ ሆይ ጓግተናል
6.
ግማሹ ሲራገፍ ሌሎች ሲሳፈሩ
የወደደውን ይዞ ይጓዛል ባቡሩ
ከታቀደው ሥፍራ ማን ይሆን የሚደርስ
ተስፋው ጌታ የሆነ የናዝሬቱ የሱስ
7.
እነማን ይሆኑ ወደቡን የሚያዩ
መሰናክሉን አልፈው ከግቡ የሚደርሱ
ይገኙ ይሆን ወይ? ዛሬም እነያሱ
የተስፋዋን ምድር በእምነት የሚወርሱ
100%
100%