ወደ መነሻ / Back to Home
መዝሙር #167 / Song #167

የልቤን በደል አይቶ ቢሆን ጌታ

english translation

ምድብ / Category: ምስጋና / Praise
ደራሲ / Author: unknown
ዓመት / Year: 2025
👁️ Views: 1
የልቤን በደል አይቶ ቢሆን ጌታ
አይሰማኝም ነበር ፀሎቴን ባንድ አፍታ
ምህረቱን ደግሞ አላራቀምና
አመሠግናለሁ ዛሬም እንደገና/2X/
1.
አምላኬ ታጋሽ ነው ሁሉም ይቻለዋል
እንደኃጢያት አይከፍል መቼ ይቸኩላል
ፈጥኖ መለሰልኝ የልቤን መሻት
እስከዘለአለም ክብር ይሁንለት/2X/
2.
በጨነቀኝ ጊዜ እግ/ርን ጠራሁ
ዓይኖቼን አንስቼ ወደ አምላኬ ጮሁ
ከመቅደሱ ቃሌን በጆሮቹ ሰማ
እንደሰው አይደለም ይድረሰው ምሥጋና/2X/
3.
ወደአንተ ለሚቀርብ አንተን ለሚጠጋ
መልስ ነህ ኢየሱስ የለም የሚያሰጋ
ምህረቱ አያልቅም ፈጥኖ ይደርስልኛል
ጌታ ሁሉን ቻይ ነው መቼ ይጨክናል/2X/
4.
ሰው ቢሆን ኖር ግን ቶሎ ያጠፋ ነበር
አንተ ግን ታጋሽ ነህ በእምነት ለሚቀርብ
ስለዚህ ልትጋ ልቤን ልክፈትለት
በሁለንተናዬ እርሱ ይንገስበት/2X/
5.
መንገድህን ለጌታ አደራ ብትሰጠው
ለርሱም ብትገዛ ተስፋ ብታደርገው
የልብህን መሻት ምኞት ይፈጽማል
እስከመጨረሻ በድል ያቆምሃል/2X/
100%
100%