1.
በደልን ይቅር የሚል አመጻን የሚያሳልፍ
ከጥፋት ሊያድናቸው በርስቱ ላይ የሚፈርድ
እንዳንተ ያለ አምላክ ማን ነው ምህረቱ የበዛ
ቅዱሳን ሲሰደዱ መከራም ሲበዛ
ርስትህን ለማላገጫ አሳልፈህ አትስጥ
የተቀደሰ መቅደስህን በጠላት አታስረግጥ
2.
የእግዚአብሔር ዕድል ፈንታ ተጽፏል ህዝቡ ነው
ሊሚያመልከው ሊያገለግለው ከግብጽ አገር ያፈለሰው
አርነቱን በባርነት ሊተካ የሚከጅለው
ይገባኛል የሚል ማን ነው? ርስቱ የእግዚአብሔር ነው
3.
እስከዛሬ ከብረሃል በአህዛብ ተፈርተሃል
የጠላትን እርግማን በረከት አድርገሃል
የአሳዳጆችን ፈረሶች በባሕር አስጥመሃል
በክንድህ ተከላክለህ ርስትህን ጠብቀሃል