ጌታ ቅደምልኝ በኑሮዬ ሁሉ
የአንተ ስለሆነ በመከራ ድሉ (2)
1.
ጌታን የሚያስቀድም በኑሮው በቤቱ
አቅፎ እንደ ደገፈው እንደ እናት አባቱ
ያ ነው የአምላክ ወዳጅ ክብሩን የማይፈልግ
በክፉ በደጉ ከቶ ማይበረግግ
2.
በትዕግሥት ጠብቁ አምላክ ይቅደም የሚል
እራሱን በውርደት ከመስቀሉ ሚጥል
ያ ነው ያምላክ ወዳጅ ምኞቱን ያሟላ
ለያዘው ቁም ነገር ከቶ የማይላላ
3.
ጌታ እንድቀድምልህ በኑሮው መከራ
በእምባው እየታጀበ ለመዝሙር ሲጠራ
ያ ነው የአምላክ ወዳጅ ክብሩን የሰቀለ
ያጋንንትን ሥልጣን በእምባው ያቃጠለ