ስላወጣሀኝ ተራራ
ስላሳለፍከኝ መከራ
ስላሻገርከኝ ማዕበል
ተመስገን እንጂ ምን ልበል
1.
ለማለፍ ሩቅ የሆነ
ተስፋዬን ያመነመነ
የወጋኝ በነጋ ጠባ
አላውቅም የት እንደገባ
2.
የዛሬ ተስፋ ጨልሞ
ለሊቱን እጅግ አርዝሞ
በጎኔ እሾህ የሆነ
ሲነጋ ወዴት በነነ
3.
መንገዴን በእሾህ የዘጋ
ወጥመዱን ለእግሬ ዘረጋ
አለፍኩኝ ከእጁ አምልጬ
የእባቡን ራስ ረግጬ
4.
አልሞትም በህይወት እኖራለሁ
የጌታዬን ስራ አወራለሁ
የሞቴን መርዶ የሰማችሁ
አለሁኝ ደስ ይበላችሁ
5.
አልሞትም በህይወት እኖራለሁ
የጌታዬን ስራ አወራለሁ
የሞቴን መርዶ የሰማችሁ
አለሁኝ ደስ ይበላችሁ