ጌታ ኢየሱስ ሆይ እጄን ያዘኝ
የማልረባ ነኝ ኃይል የሌለኝ
1.
የማደርገው ሲገባኝ ግራ
ኑሮ ሲሆንብኝ መራራ
የምታጣፍጥ ጨው ቅመሜ
ርቀህ አትቁም ከአጠገቤ
2.
እኔ የያዝኩ እንደሁ እጅህን
መከተል ሲያቅተኝ እርምጃህን
ድንገት እለቅሃለሁ ደካማ ነኝ
አንተ አትደክምም እጄን ያዘኝ
3.
በጨለማው አለም ስመላለስ
ተሰነካክዬ እንዳላለቅስ
መንገዴን አሳየኝ ብርሃን ሆነህ
ጺዮን አግባኝ እጄን ይዘህ
4.
ሥጋ ለባሹ ሳይ ባይኖቼ
ሰውን ይዤ ስሮጥ በእጆቼ
የተሰባበርኩት ቁስሌ አልሻረም
አንተው ይዘኝ ለዘላለም