1.
በጌታዬ በክርስቶስ
ቃል ላይ ቆሜ
ለዘላለም እርሱን ሳመሰግነው
ክብር በላይ ይሁን
እያልኩ ስዘምር
በአምላክ ተስፋ ቃል ቆሜ
በጌታ ቃል በመድህኔ ቃል
ኪዳን ላይ እቆማለሁ
በጌታ ቃል
በመድህኔ ቃል ኪዳን እቆማለሁ
2.
በማይወድቀው የጌታ
ቃል ላይ ቆሜ
ፍርሃትና ጥርጣሬ ሲነፍስ
በርሱ ቃል አሸናፊ እሆናለሁ
በአምላክ ተስፋ ቃል ቆሜ
3.
አሁን በማየው ተስፋ
ቃል ላይ ቆሜ
ለኔ ንፁህ ፈዋሽ
የሆነውን ደም
አገኘሁ በየሱስ ይህን ነፃነት
በአምላክ ተስፋ ቃል ቆሜ
4.
በጌታ በክርስቶስ ቃል
ላይ መታመን
በፍቅሩም ከራር
ገመድም መታሠር
በመንፈስ ሰይፍም
ሁልጊዜ ድል መንሳት
በአምላክ ተስፋ ቃል ቆሜ