1.
በራቀው ኮረብታ
መስቀል ይታየኛል
የየሱስ መከራ መስቀል
ከሁሉ ይልቅ ያ
መስቀል ደስ ይለኛል
ለዓለም ሞቱን ያሣያል
ስለዚህ ልውደደው መስቀሉን ከኃጢዓት ሁሉ ያዳነኝን እጠማጠማለሁ መስቀሉን ለዘውድም እለውጠዋለሁ
2.
ያ መስቀል ዓለሙ
በሙሉ የናቀው
የሚያስደንቅ መድኃኒት ነው
የሱስን የሰማይ
ቤቱን ያስለቀቀው
እኛ ልንድንበት ነው
3.
ያ አሮጌ መስቀል
ደሙ ያጠለቀው
እጅግ አምሮ ይታየኛል
በዚህ መስቀል የሱስ
ነው የተሰቀለው
ለዓለሙ ኃጢዓት ሲል
4.
ያን አሮጌ መስቀል
እኔ አምነዋለሁ
ስድቡንም እሸከምአለሁ
አንድ ቀን ከሰማይ
ቤቱ ይጠራኛል
ክብሩንም ያካፍለኛል