1.
ኦ ከእግዚአብሔር ጋር ልራመድ
ኄኖክ በሔደበት መንገድ
ደካማ እጄን ይዘህ ምራኝ
በጣፋጭ ድምፅህ ምከረኝ
መንገዱ እንዳይጠፋብኝ
መድኅን የሱስ አትለየኝ
2.
አልችልም ብቻዬን ልሔድ
ሲንዣበብ የሰማይ ሞገድ
ተጠምደው ሣል ሺህ ወጥመዶች ከበውኝ ሳል ሺህ ጠላቶች
ፀጥ አርግና ይህን ሞገድ
ኦ ጌታ ሆይ አብረን እንሒድ
3.
እጄን በጅህ ላይ አድርጌ
የምድርንም ተድላ ንቄ
በድፍረት እራመዳለሁ
መስቀልህን እሸከማለሁ
ወደ ጽዮን በር እስክደርስ
ጌታ ሆይ አብረን እንጓዝ