1.
ጌታ ሆይ ናፍቄህ አለሁ
ደካማ ዕውር ሣለሁ
ኃይልና ማየት አገኘሁ
ባንተ እታመናለሁ
በየሰዓት በየሰዓቱ
መድኃኒቴን እሻዋለሁ
በየሰዓት በየሰዓት
መድኃኒቴን እሻለሁ
2.
የገርነት ልብስ አልብሰኝ
ኃጢዓት ስላቆሸሸኝ
ደካምነቴን አወቅሁኝ
አምላካዊ ኃይል ስጠኝ
3.
ብትመራኝ እድናለሁ
ብለይህ እወድቃለሁ
ሁን ከኔ ጋር በችግሬ
አንተ ሕይወት ብርሃኔ
4.
ለወደፊት የሚመጣ
ኃዘን ወይም ደስታ
ካንተ ሊለየኝ አይችልም
የኔ ተስፋ አንተ ነህ