1.
የሕይወቴ ገዥ ላንግሥህ
ምስጋናህን ልስጥህ
እንዳልረሣ ሾህ አክሊልህን
አስታውሰኝ ቀራንዮን
እንዳልረሳ ጌትሰማኔን
እንዳልረሳ ጭንቀትህን
እንዳልረሳውም ፍቅርህን
አስታውሰኝ ቀራንዮን
2.
አመልክተኝ መቃብርህን
ያለቀስህበትን
መላእክትህ
ነጭ ልብስ ለብሰው
ሲጠብቁህ ቁመው
3.
እንደ ማርያም
በጭንቅ ጊዜ
ስጦታ ላምጣልህ
ባዶ መቃብሩን አሣየኝ
አስታውሰኝ ቀራንዮን
4.
ለመሸከም የኔን መስቀል
ፈቃደኛ አርገኝ
የኃዘን ፅዋን ልካፈል
አንተን በመከተል