1.
የሱስ ሆይ ወደድሁህ የኔ ነህና
ኃጢአቴንም ሁሉ እተወዋለሁ
ክቡር አዳኜና መድኃኒቴ ነህ
ከቀድሞውም ይልቅ አሁን ወደድሁህ
2.
ፊት ስለወደድኸኝ እኔም ወደድሁህ
ኃጢአቴን በቀራንዮ ተሸከምህ
ስለ መጨነቅህ እወድህአለሁ
ከቀድሞውም ይልቅ አሁን ወደድሁህ
3.
በሞትና ህይወት እወድህአለሁ
እያመሰገንሁህ ነፍሴ እስካለች
ሞትም ሲመጣብኝ እንዲህ እላለሁ
ከቀድሞውም ይልቅ አሁን ወደድሁህ
4.
በሰማይ ፍጻሜ በሌለው ደስታ
አንተን ከዚያ ሆኜ አወድሣለሁ
መዝሙሬን በደስታ እዘምር አለሁ
ከቀድሞውም ይልቅ አሁን ወደድሁህ